Friday, October 31, 2014

ሰበር ዜና –አብርሃ ደስታ; ሀብታሙ አያሌው; የሽዋስ አሰፋ ; ዳንኤል ሺበሺ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው


አብርሃ ደስታ የሁለት ድርጅቶች አባል ነው የሚል ክስ ተመስርቶበታል
• ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዟል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በልደታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በተሰየመው ችሎት 10 ተከሳሾች በፌደራል አቃቢ ህግ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ100 ገጽ በላይ የክስ ቻርጅ የተነበበላቸው ሲሆን ከክስ ቻርጁ ጋር ከ300 ገጽ በላይ የምርመራ ሰነድ ቀርቦባቸዋል፡፡
የክሱ መዝገብ የተከፈተው ዘላለም ወርቃገኘሁ በተባለውና ‹‹የግንቦት 7 አመራር ነው፡፡›› ተብሎ ክስ በተመሰረተበት ግለሰብ ሲሆን በዚህ የክስ መዝገብ የተካተቱትም፡-
1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ
2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው
3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ
5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ
6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ
7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን
8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ
9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ
10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው
ለሁሉም ተከሳሾች ከዛሬ በፊት ክስ እንዳልደረሳቸውና ዛሬ ፍርድ ቤት ውስጥ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ በችሎቱ 6ኛ ተከሳሽ ከሆነው ዮናታን ወልዴ በስተቀር ሁሉም ያለ ጠበቃ የቀረቡ ሲሆን ጠበቃዎቹ ያልቀረቡበት ምክንያትም ጠበቆቹ ደምበኞቻቸው የሚቀርቡበት ቦታና ጊዜ ስላልተነገራቸው እንዲሁም ቀደም ብለው እንዳይገናኙ በመደረጋቸው መሆኑን አቶ ኃብታሙ አያሌው ችሎቱ ላይ ተናግሯል፡፡
ከሳሹ የፌደራል አቃቢ ህግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ እና የጸረ ሽብር ህግ ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ክሶቹ በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጭብጥ ‹‹ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር በጋራ በመስራት›› የሚል ሲሆን ‹‹ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ የመንግስትን መሰረተ ልማት በማፈራረስ፣ ህዝብን ለአመጸ በማነሳሳት መንግስትን መለወጥ አላማው አድርጎ ከሚሰራውና ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራው ቡድን ጋር አባል በመሆንና በወንጀል ድርጊቶች በመሳተፍ›› በሚል ቀርቧል፡፡
ሁለተኛው የክስ ጭብጥ ‹‹የሽብር ቡድን አመራር በመሆን›› የሚል ሲሆን በተለይም የአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹የሽብር ቡድኑ አመራር በመሆንና አባል በመመልመል›› በሚል የክስ ጭብጥ ቀርቦበታልል፡፡
ከ2-5ኛ የክስ መዝገብ የሚገኙት ማለትም ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታና የሸዋስ አሰፋ ‹‹ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ከለላ በማድረግ ግንቦት 7 የተባለውን የሽብር ቡድን አላማ ለማሳካት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ፋሲል የኔ ዓለምና ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር በስልክ በመነጋገርና በማህበራዊ ድህረ ገጸ የተለያዩ መልዕክቶችን ተለዋውጠዋል›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ አብርሃ ደስታ ከግንቦት 7 በተጨማሪ ‹‹ደምኢት የተባለ ቡድን አባል ነው፡፡›› የሚል ክስ ቀርቦበታል፡፡
በስተመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አንደኛው ረቡዕ ጥቅምት 26/2007 ዓ.ም 3 ሰዓት ተከሳሾቹ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ጋር ተማክሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለተኛነት ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ቀደም ሲል ለአራት ወራት ወደቆዩበት ማዕከላዊ እስር ቤት እንዳይመለሱ ፍርድ ቤቱን ስለጠየቁ ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (3ኛ) እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተከሳሾቹ ትናንት ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ የነበር ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ጠዋት ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ተወስደው የነበረ ቢሆንም እንደገና ወደማዕከላዊ ተመልሰው ከሰዓት እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡

Monday, October 27, 2014

ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት






የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ቀን በዋለው ችሎት 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ ፍትህን ሲያሳትም የነበረውና ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ማስተዋል ህትመትና ማስታወቂያ በ10 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበታል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅም 3/2007 ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አሁን የተፈረደበት በትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በአንደኛው ክስ ነው ተብሏል፡፡ የጥፋነኝነት ክሱ በተነበበት ወቅት ግን ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል ብሎ ጽፏል፡፡›› በሚል ጥፋተኝ ነው ተብሏል፡፡

አቃቢ ህግ የቅጣት ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ሆነ ጠበቃው የቅጣት ማቅለያ አላቀረቡም፡፡ በሌላ በኩል የጋዜጠኛው ጠበቃ አምሃ መኮንን ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስታውቀዋል፡፡

‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ጥያቄ ያነሳው የአንበሳ ከተማ አውቶቡስ ሰራተኛ ታሰረ::


- ‹‹ግንቦት 7 ብሎ ጠረጴዛ ላይ ጽፏል፡፡›› የሚል የሀሰት ክስ በፍርድ ቤት ተመስርቶበታል።
- ‹‹ደርግንም ሆነ ምኒልክን እናውቃቸዋለን፡፡ እናንተ ስለ እነሱ መጥፎውን ከምትገልጹልን እንደ 97 እንደማትገድሉና ነጻና ፍትሃዊ ምትጫ እንደምታደርጉ ንገሩን፡፡››
- ስልኩን እና የማስታወሻ ደብተሩን ካድሬዎች እና ደህንነቶች እየተጠቀሙበት ነው።
-ስልጠናውን በደንብ አልተከታተላችሁም በሚል ተጨማሪ 8 ቀን ቅጣት ተጥሎባቸዋል።



ገዥው ፓርቲ በሚሰጠው የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ጥያቄ የጠየቀና ስርዓቱን የተቸ የአንበሳ አውቶቡስ ድርጅት ሰራተኛ ታሰረ፡፡ ፋንታሁን የተባለው የአንበሳ ከተማ አውቶቡስ ሰራተኛ በስልጠናው ወቅት ጥያቄዎቹን በማንሳቱና ስርዓቱን በመተቸቱ መታሰሩን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

በስልጠናው ወቅት ስላለፉት ስርዓቶች በተነሳበት ወቅት ‹‹ደርግንም ሆነ ምኒልክን እናውቃቸዋለን፡፡ እናንተ ስለ እነሱ መጥፎውን ከምትገልጹልን እንደ 97 እንደማትገድሉና ነጻና ፍትሃዊ ምትጫ እንደምታደርጉ ንገሩን፡፡›› ሲል አስተያየት የሰጠው ፋንታሁን ይህና ሌሎች አስተያየቶቹ መስሪያ ቤቱ ውስጥ የሚሰሩ የኢህአዴግ ካድሬዎችን እንዳስቆጣ ገልጾአል፡፡ ስብሰባው ካለቀ በኋላም ረቡዕ ጥቅምት 13/ 2007 ዓ.ም አንበሳ አውቶቡስ ድርጅት ውስጥ የሚሰሩ የኢህአዴግ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ደህንነቶች እንደያዙት ገልጾአል፡፡

በስልጠናው ወቅት ጥያቄ በመጠየቁና ትችት በመሰንዘሩ አንበሳ አውቶቡስ ውስጥ የሚሰሩ የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ‹‹ግንቦት 7 ብሎ ጠረጴዛ ላይ ጽፏል፡፡›› የሚል የሀሰት ክስ እንደከፈቱት ፋንታሁን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

ከታሰረ በኋላ ስልኩና የግል አጀንዳውን የተቀማ ሲሆን ስልኮቹን መስሪያ ቤቱ ውስጥ ያሉት ካድሬዎች እየተጠቀሙበት እንደሆነና ስልክ ሲደወልም እያነሱ እያነጋገሩ እንደሆነ መረጃ እንደደረሰው ገልጾልናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስለ አገሩ ወቅታዊ ሁኔታ የጻፋቸውንና ሌሎችንም ጉዳዮች ያሰፈረበትን የግል ማስታወሻው ደህንነቶች ‹‹ምን ማለት ናቸው? ከማን ጋር ነው የምትገናኘው?›› እያሉ ጫና እያሳደሩበት መሆኑን አስታውቋል፡፡

ስልኩና ማስታወሻ በካድሬዎችና በደህንነቶች እጅ በመግባቱ ‹‹የግል ማስታወሻዬና ስልኬን ደህንነቶችና የኢህአዴግ ካድሬዎች እየተጠቀሙበት በመሆኑ እኔ ግንኙነት ከሌለኝ አካል ጋር ግንኙነት እንዳለኝ አሊያም ያልጻፍኩትን የጻፍኩ በማስመሰል እንደማይከሱኝ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡›› ሲል ፋንታሁን ስጋቱን ገልጾአል፡፡

ፋንታሁን በተለምዶ ችሎት ተብሎ በሚጠራው ቀጨኔ መዳህኒያለም አካባቢ በሚገኝ ወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የሚገኝ ሲሆን ነገ ማክሰኞ/ ጥቅምት 18 ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ ይጠበቃል፡፡

የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን ለ11 ቀናት የወሰዱት የከተማ አውቶቡስ ድርጅት ሰራተኞች ስልጠናውን በደንብ አልተከታተላችሁም በሚል ተጨማሪ 8 ቀን ቅጣት ተጥሎባቸው ስልጠናውን ዳግመኛ እንደወሰዱ ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወሳል፡፡

በአገር ላይ የሚመጣ አደጋን አቅልሎ የማየት ያልሰለጠነ አስተሳሰብ፤

Add caption

ታዳጊ አገሮችን በሙሉ የሚያመሳስላቸው አንድ ግርም የሚለኝ ነገር ከገደል አፋፍ ቆሞ ገደሉን መናቅ፣ ከአደጋ ጫፍ ቆሞ አደጋን ማቃለል፤ ከዚያም ከገደሉ ወድቆ መሰበር፣ በአደጋው ተጠራርጎ መወሰድ። ይህ ሐሳብ በርግጥ ፍንትው ብሎ የታየኝ የማሌዢያ አውሮፕላን በዩክሬይን ሰማይ ላይ በሚሳኤል በጋየበት ጊዜ ነበር። ሁላችሁም እንደምታስታውሱት የሰው አካል ቁርጥራጭ ከሰማይ ይዘንብ እንደነበር እማኞች ሲናገሩ መልክተናል።

ታላላቆቹ የዜና አውታሮች ራሺያ ላይ አተኩረው ነገሩን በዚያ ፈፀሙት አንጂ «አውሮፕላኑ በጦርነት ሰማይ ላይ ለምን ሄደ?» የሚለውን የሚያነሱ ሰዎችም ተደምጠዋል። ብዙ አየር መንገዶች አቅጣጫቸውን ቀይረው በሌላ መስመር መሔድ ከጀመሩ ቆይተው ነበር። የሳንቲም ስባሪ ለማትረፍ አንድም በማሌዢያኛ «አቦ አታካብዱ» ብለው ሳይሆን አይቀርም በዚያ በታዳጊ አገር አስተሳሰብ መንገዳቸው ሳይቀይሩ ቀሩ።


«የእባብ ጉድጓድ በጅል ክንድ ይለካል» እንደሚባለው የዩክሬይን አየር በማሌዢያ አውሮፕላን ክንድ ሲለካ ጅልም እጁ አይተርፍ፣ አውሮፕላኑም አልተረፈ። ተመሳሳይ ነገር እነሆ ሊከሰት ነው። ኢትዮጵያ በበኩሏ 200 ነርሶች ወደ ኢቦላ ዞን (Ebola ZOne) ልትልክ ጀብደኛ ውሳኔ ወስናለች። የማሌዢያ ውሳኔ።

ኢቦላ ምዕራብ አፍሪካን ምን እያደረገ ነው? ከበሽተኛው በሚወጣ ፈሳሽ በሚተላለፈው በዚህ በሽታ የአገራች ኢኮኖሚ እንዴት እንዴት እየሆነ ነው? የዚያ አገር ዜጋ የሆኑ በማለው ዓለም የሚኖሩ ሰዎች እንዴት እየታዩ ነው? ምን ዓይነት ችግር እየገጠማቸው ነው? አይበለውና በሽታው አገራችን ቢገባ ዘመዶቹን በማስታመም የሚታወቅ የአገራችን ሰው እንዴት ባለ አደጋ ላይ ይወድቃል? የትኛው ሆስፒታል በርግጥ ብቁ ነው? መቸም በፌዴራል ፖሊስ ዱላ አታስቆሙት ነገር። «የሕዳር በሽታን» በአገራችን በ21ኛው ክ/ዘመን ልታመጡብን ካልሆነ በእውነቱ ምን ሌላ ምክንያት ይኖራችኋል? በዓለም ላይ በሕክምና አያያዛቸው ጥራት የተመሰገነላቸው ብዙ አገሮች አሉ። ኢቦላን በረዓድ እያዩት ነው። ሕዝቡ ገና ስሙን ሲሰማ ሽብር ይይዘዋል። አንድ ሰው ቴክሳስ ግዛት በበሽታው በመሞቱ መላው አሜሪካ ከሥሩ ነው የተነቃነቀው። በርግጥ እነርሱ ፈሪዎች ስለሆኑ እኛ ጀግንነት ይዞን ይሆን? የሚመጣውን ጉድ ስለሚረዱት ነው።

ይህንን ያልሰለጠነ አስተሳብ እንዴት ማስለቀቅ ይቻል ይሆን? አለመሰልጠን ወንጀል አይደለም ነገር ግን አገር ላይ ሊያመጣ የሚችለውን አደጋ እያወቁ ለጋ ወጣቶችን ወደ እሳት መላክ ግን ሌላ ዓላማ እንዳለው ነው የሚረዳኝ። ምናልባት በበሽታው የሚገኝ ትርፍ እንዳለ እንጃ። ፈጣሪ ሕዝቡን ይታደገዋል። ለእናንተ ግን እንጃ!!!

ኤፍሬም እሸቴ

Sunday, October 26, 2014

Dictators free themselves but they enslave the people!




I’m sorry, but I don’t want to be an emperor. That’s not my business. I don’t want to rule or conquer anyone. I should like to help everyone - if possible - Jew, Gentile - black man - white. We all want to help one another. Human beings are like that. We want to live by each other’s happiness - not by each other’s misery. We don’t want to hate and despise one another. In this world there is room for everyone. And the good earth is rich and can provide for everyone. The way of life can be free and beautiful, but we have lost the way.


Greed has poisoned men’s souls, has barricaded the world with hate, has goose-stepped us into misery and bloodshed. We have developed speed, but we have shut ourselves in. Machinery that gives abundance has left us in want. Our knowledge has made us cynical. Our cleverness, hard and unkind. We think too much and feel too little. More than machinery we need humanity. More than cleverness we need kindness and gentleness. Without these qualities, life will be violent and all will be lost....


The aeroplane and the radio have brought us closer together. The very nature of these inventions cries out for the goodness in men - cries out for universal brotherhood - for the unity of us all. Even now my voice is reaching millions throughout the world - millions of despairing men, women, and little children - victims of a system that makes men torture and imprison innocent people.


To those who can hear me, I say - do not despair. The misery that is now upon us is but the passing of greed - the bitterness of men who fear the way of human progress. The hate of men will pass, and dictators die, and the power they took from the people will return to the people. And so long as men die, liberty will never perish. .....


Soldiers! don’t give yourselves to brutes - men who despise you - enslave you - who regiment your lives - tell you what to do - what to think and what to feel! Who drill you - diet you - treat you like cattle, use you as cannon fodder. Don’t give yourselves to these unnatural men - machine men with machine minds and machine hearts! You are not machines! You are not cattle! You are men! You have the love of humanity in your hearts! You don’t hate! Only the unloved hate - the unloved and the unnatural! Soldiers! Don’t fight for slavery! Fight for liberty!


In the 17th Chapter of St Luke it is written: “the Kingdom of God is within man” - not one man nor a group of men, but in all men! In you! You, the people have the power - the power to create machines. The power to create happiness! You, the people, have the power to make this life free and beautiful, to make this life a wonderful adventure.


Then - in the name of democracy - let us use that power - let us all unite. Let us fight for a new world - a decent world that will give men a chance to work - that will give youth a future and old age a security. By the promise of these things, brutes have risen to power. But they lie! They do not fulfil that promise. They never will!


Dictators free themselves but they enslave the people! Now let us fight to fulfil that promise! Let us fight to free the world - to do away with national barriers - to do away with greed, with hate and intolerance. Let us fight for a world of reason, a world where science and progress will lead to all men’s happiness. Soldiers! in the name of democracy, let us all unite!


Charlie chaplin

የኖርዌይ ኦስሎ ወጣቶች ስለአገራቸው ውይይት አካሄዱ



የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የወጣቶች ክፍል ቅዳሜ ጥቅምት 10/2007 ዓም(ኦክቶበር 25/2014) “ለአገር እድገትና ለድሞክራሲ ግንባታ የወጣቶች አስትዋጾ” በሚል ሰፊ ውይይት ከ15:00 እስከ 18:00 ስዓት ተካሄደ።

የመግቢያ ንግግሩ በድርጅቱ ህዝብ ግንኙነት በአቶ አቢ አማረ የውይይቱን ዓላማና አስፈላጊነት ለተሳታፊው በመግለጽ ወጣቶች ውይይቱ ውጤት ሊያመጣ በሚችል መልኩ እንዲካሄድ አጽንኦት ሰጠው ውይይቱ ቀጥሏል።

በመቀጠልም የአንድ አገር ቀጣይነት ያለው እድገት የሚለካው በአላት ሃብትና ንብረት ብቻ ሳይሆን ያንን ተረክቦ በአደራ ለትውልድ ማስተላለፍ የሚችል ትውልዳዊ ትስስር መኖርና ይህንንም እንደ ድልድይ ሆኖ ከአንዱ ትውልድ ወደቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፈው ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል እንደሆነ፤ በማንኛውም አገር፣ ጊዜና ዘመን እያንዳንዱ ተተኪ ትውልድ የአገሩ ወራሽ፣ ተተኪና ተረካቢ፣ ጠባቂና ለሚቀጥለውም ትውልድ የማውረስ፣ የማስተላልፍና የማስረከብ ኃላፊነትና ግደታ እንዳለበት፤ ወጣት ለአንድ አገር በሦስቱም ዘርፍ ማለትም በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብታዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ማድረግ እንደሚችል ተረድቶ ወጣቱ ትውልድ በዓላማ፣ በቁርጠኝነት፣ በዕቅድና በመደራጀት ለአገር እድገት፣ ነጻነት፣ፍትህና ዲሞክራሲ መታገልና ለውጥ ማምጣት እንዳለበት በክፍሉ ተወካይ በወጣት ይበልጣል ጋሹ ለውይይት እንደ መነሻ ባቀረበው ሃሳብ ላይ ገልጿል። እንዲሁም የወያኔን አስከፊ፣ ዘረኛና አምባገነናዊ ሥርዓት ለማስገወገድ ወጣቱ ትውልድ የበኩሉን ሃላፊነት ወስዶ ይህን ለአገርና ለህዝብ መቆም እንዳለበት በመግለጽ የውይይት ሃሳቦችን አስቀምጦ ስዓቱን ለውይይት ክፍት አድርጓል።

በውይይቱም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ወጣቱ ለክፉም ለመልካምም የራሱ የሆነ ትልቅ አገራዊ ታሪክ እንዳለው በመግለፅ ወጣቱ እንዴት መታገልና ለውጥ ማምጣት እንደሚችል ገንቢ አስትያየቶች፣ ምክሮችና አቅጣጫ ተሰጠዋል። ከተነሱትት ሃሳቦች መካከልም በበቂ ሁኔታ መደራጀት፣ በእውቀት እራስን ማብቃት፣ አገራዊ ስሜት መላበስ፣ታሪክን ጠንቅቆ ማዎቅ፣ አንድነት መፍጠር፣ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ስልታዊ እቅድ መከተል፣ አቀራረባችንን እና ትኩረታችን መለየት፣ ቀጣይነት ያላቸው የውይይት መድረኮችን ማዘጋጀት እና ክፍሉን ማደራጀት ከተነሱት አበይት ሃሳቦች መካከል ነበሩ። በተጨማሪም ክፍሉ ከሌሎች የወጣት ህብረት ጋር ግንኙነት በመፍጠር ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ ወጣቱን ይበልጥ ማንቃትና ፖለቲካዊ አድማሱን ማስፋትና የወያኔን ጨቋን መንግሥት ሊታገል የሚችልበትን አቅጣጫ ማሳየትና መንደፍ ተገቢ መሆኑን አጽንኦት ተሰጦበታል

Friday, October 24, 2014

ምጽዓት ( መስፍን ወልደ ማርያም)


መስፍን ወልደ ማርያም / መስከረም 2007

በግዞትም ቤት አደባባይ ታስሮ ሳለ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደኤርምያስ መጣ፡– ሂድ ለኢትዮጵያዊውም ለአቤሜሌክ እንዲህ በለው፤ — የእሥራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤- እነሆ ለበጎነት ሳይሆን ለክፋት ቃሌን በዚህች ከተማ ላይ አመጣለሁ፤ በዚያም ቀን በፊትህ ይፈጸማል፤ በዚያ ቀን አድንሃለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር፤ በምትፈራቸው ሰዎች እጅ አልሰጥህም፤ ፈጽሜ አድንሃለሁ፤ ነፍስህም እንደምርኮ ትሆንልሃለች እንጂ በሰይፍ አትወድቅም፤ በበእኔ ታምነሃልና ይላል እግዚአብሔር፡፡ ትንቢተ ኤርምያስ 39/15-18

ኑዛዜ ኤርምያስን አነበብሁ፤ጉድ ነው! አንድ የማውቀውን ነገር አረጋግጥሁ፤ ብዙ የማላውቃቸው ነገሮችን አወቅሁ፤ የማውቀው ነገር ሂሳብ የተማረ ሰው ምን ጊዜም ጭፍን ሎሌ መሆን የማይችል መሆኑን ነው፤ሂሳብ የተማረውን ሰው ለጭፍን ሎሌነት የሚቀጥረው ሰው ግን አንጎሉ የፈረጠ ነው፡፡

የማላውቃቸው ነገሮች ዝርፊያ በየፈርጁ! በቃሊቲ ወህኒ ቤት የትምህርት ቤት የነበረ ሕንጻ ወደእስር ቤት መለወጡን አይቼ ነበር፤ አሁን ደግሞ የሕዝብ ትምህርት ቤት ለግለሰብ መሸጡን አወቅሁ፤ ጡንቻ ነው እንጂ ትምህርት ምን ዋጋ አለው! ይህ ሁሉ ዝርፊያ፣ ይህ ሁሉ ወንጀል ሲፈጸም ሌላው ሁሉ ጮሆ አቤት ለማለት እንኳን የማይደፍር ሆኖ ነው ወይስ የሕግ አስከባሪ በአገሩ ጠፍቶ ነው? ድፍረቱን አጥፍተውት ከሆነ በከበደ ሚካኤል ብእር ፋሺስቱ የተናገረው ልክ ነበር ማለት ነው፤–

መሬት የሁሉ ነች ባለቤት የላትም!

ኃይለኛ እየሄደ ያስገብራል የትም፤

መሬት ባለቤት ከሌላት ሰዎች አገር የላቸውም ማለት ነው፤ አገር የሌላቸው ሰዎች ዶላር ይዞ ለመጣ ቤታቸውንና መሬታቸውን እንዲያስረክቡ ይገደዳሉ፤ ሕገ መንግሥቱ መሬት የሕዝብና የመንግሥት ነው ስለሚል ባለዶላር ወይም ባለሀብት ሕዝብ የሚለውን ይተካል።

ኑዛዜ ኤርምያስን ያነበበ የወያኔ ባለሥልጣኖችን ራቁታቸውን ያያቸዋል፤ ካልዋሸ ራሱንም ራቁቱን ቆሞ ያየዋል፤ ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ ደጋግሜ እንዳልሁት ጨቋኝና ተጨቋኝ ተደጋጋፊዎች ናቸው፤ አንዱ ያላንዱ አይኖርም፤ በኑዛዜ ኤርምያስ ላይ ጎልቶ ለሚታየው የጨቋኞቹ ቆራጥነትና ጭካኔ ጉልበቱን ከየት አገኙት ቢባል መልሱ ቀላል ነው፤ ከተጨቋኞቹ ተንጋልሎ ጭቆናን ከመቀበል ችሎታ ነው፤ድፍረታቸውን አደንቃለሁ፤ድፍረታቸው ወደወንበሩ ስቧቸው ወጡበትና (ተቀመጡበት እንዳልል አልተመቻቸውም፤) ዘመኑ የፍርሃት፣ እንቅልፍ አጥቶ የመባነን፣ የመደናበር ሆኖባቸዋል፤ የፍርሃት በሽታ ዓይንን ይሰውራል፤ ጆሮን ይደፍናል፤ አቅምን እንዳያውቁ ያደርጋል፤ በዚህ ሁሉ ምክንያት ከማይችሉት ጋር ያላትማል።

ምጽዓት የሚል ግጥም አለኝ፤ ትዝ አለኝ!

ባሳብ ባሕር ዘፍቆ የሰው ልጅ ሲጨነቅ፣

ሃይማኖት ሲራባ ፍልስፍና ሲረቅ፣

ነፍስ እምነትን አጥታ፣ መንምና በችጋር፣

እውነቱ ሲያሳፍር፣ ሲያስጠላ፣ ሲያስመርር፣

ኃይል ክፋት ሲሆን የደካሞች ጭነት፣

ፍቅር ጥምቡን ጥሎ ሲገዛ እንደኩበት፣

ፍርሃት ትእግስት ሆኖ ድንቁርና ኩራት፣

ውርደትም ትሕትና ጮሌነትም እውቀት፣

ትምህርትም ጌጥ ሆነ ያውም የተውሶ፣

ስንፍናም ጨዋነት ሰውነት ረክሶ፣

ማተብ ክርስትና ነጭ ጥምጥም ክህነት፣

ሀብት ብልጽግና መቾት ትልቅነት/

ምኞት ተስፋ ሆኖ መቃብርም ኑሮ፣

እንጉርጉሮው ዘፈን፣ ዘፈኑ እንጉርጉሮ፣

ባዳ ሆነ ዘመድ ባለቤቱ እንግዳ፣

ሆድም አምላክ ሆነ አውሬውም ለማዳ፣

ገንዘብ ዳኛ ሲሆን ወንጀል ከሳሽ ሆኖ፣

ግብዝነት ደላው ጽድቅ ተኮንኖ!

ወጣትነት ጫጨ እርጅና እየለማ፣

የኋሊት መገስገስ የጊዜው ዓላማ!

ከራስ በላይ ነፋስ ትልቁ ሃይማኖት፣

ዘረፋን ሲያውጀው ቂም ሲያስረግዝ ጥቃት፣

ዓይን አያይም አሉ፤ ጆሮም አያዳምጥ!

ተለጉሞ አንደበት ሁሉም ይዞታል ምጥ!

በቁንጣን በስካር ጥቂቶች ሲንሩ፣

ብዙዎቹ ደግሞ በረሃብ መንምነው በቁንጫ ሲያርሩ.

የደሀ እንባ ሲጎርፍ መሬቱ ሲሸበር፣

ፍትሕ በሌለው ፍርድ ሚዛኑ ሲሰበር፣

ዝብርቅርቁ ወጣ!

ህይወት ትርጉም አጣ!

ኧረ የት ነው ጉዞው? ዓላማው ምንድን ነው?

ቀድመው የሄዱትን ምነው አናያቸው!

የት ገቡ? የት ጠፉ? ፋና እንኳን አይታይ፤

ብልጭ የሚል የለ፤ ከመሬት ከሰማይ!

መንገዱ ጠበበ ትርምስምሱ በዛ፤

እሪታው ኡኡታው ቀለጠ እንደዋዛ፤

መሬቱም ዓየሩም በክፋት ጠነዛ፤

ጥላቻና ቂሙ በሰፊው ተነዛ፤

እምቢልታው ሲጣራ፣ ነጋሪት ሲያገሳ፣

የአለው ሁሉ ሞቶ የሞተው ሲነሣ፣

ምጽዓት መድረሱ ነው፤ ሊስተካከል ነው ፍርድ፤

በግና ፍየሉ ሊለዩ በገሀድ!

የሚጠየቅ ሰው ቢኖር አንድ ቀላል ጥያቄ መጠየቅ እፈልግ ነበር፡- የዝርፊያው ፉክክር የት ለመድረስ ነው? በአንድ ቤተ ክርስቲያን ወይም መስጊድ ጓሮ ሁለት ሜትር በአንድ ሜትር ክፍል የሬሳ ቤት ለማሠራት? አይ ሰው!- 

Thursday, October 23, 2014

መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ ከጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ



‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ሰው ሆኖ ለእስር ይወጣል››
‹‹ተመስገን፣ የህዝብ ልጅ ነው፤ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ‹‹ስለተመስገን ደሳለኝ ሃሳቤን አስተላልፍልኝ›› ካለኝ የተወሰደ
ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ዕለት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆነውን አቶ አንዷለም አራጌን በ2007 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ላገኛቸው ችዬ ነበር – ለአቤል አለማየሁ ጋር፡፡ ባለፈው ሳምንት የ‹‹ባንዲራ ቀን›› በተከበረበት ዕለት ቃሊቲ ከወዳጄ እዩኤል ፍስሐ ጋር ሄጅ እነስክንድርን መጠየቅ ሳንችል ተመልሰን ነበር፡፡
የሆኖ ሆኖ፣ ከእስክንድር ጋር ለ15 ደቂቃ ያህል ለማውጋት ችለን ነበር፡፡ እስኬው፣ ሁሌም መንፈሱ ጠንካራ ነው፡፡ ሰኞም ያ አስደማሚ ጥንካሬው፣ ትህትናው፣ እውነተኛ ቅንነቱ፣ ብርታቱ፣ ቀናኢነቱ…አብረውት ነበሩ፡፡
ሰዓት ደርሶ ከእስክንድር ጋር ቻው ከተባባልን በኋላ ‹‹ኤልያስ፣ አንዴ ላናግርህ›› ብሎ ከጠራኝ በኋላ ‹‹እባክህ አንድ መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ አስተላፍልኝ›› አለኝ፡፡ እስንክድር፣ ሁሌ ሀሳቤን አስተላልፍልኝ ሲለኝ ግልጽነቱ እጅግ ይማርካል፡፡
‹‹እሺ›› አልኩት››
‹‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ጥሩ ሰው ሆኖ ከእስር ይወጣል፡፡ ተመስገን የህዝብ ልጅ ነው፡፡ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ፡፡ እስሩ ስለሀገሩ ያበረታዋል፤ ያጠነክረዋል፡፡ ብዙ ነገር እንዲረዳ ያደርገዋል፡፡ ሰዎች ይታሰሩ እያልኩ አይደለም፡፡ ይሄ አንዱ የሰላማዊ ትግል መስራት ውጤት ነው፡፡ በለውጥ እና በትግል መስመር ላይ ያሉ ኢትዮጵኖች መታሰራቸው ነገ ለውጥ ያመጣል፡፡››
ካለኝ በኋላ ለሁሉም ‹‹እወዳችኋለሁ፣ አከብራኋለሁ፣ በተሰማራችሁበት የህይወት መስመር፣ በሰላማዊ መንገድ በርትታችሁ ለለውጥ ታገሉ!›› በልልኝ ብሎኛል፡፡
እኔም ዛሬ ‹‹የሀገሪቱን ህዝቦች አንድነት እንዲፈርስ እና በሀገሪቱ ሕዝቦች መካከል ጸብና ቁርሾ እንዲፈጠር በማሰብ …›› የሚል ከባድ ክስ ብቀበልም የእስክንድርን መልዕክት ለማስተላለፍ አልተቆጠብኩም፡፡
ፍቅር ያሸንፋል!
Elias Gebru Godana

David Cameron writes to Hailemariam Desalegn



David Cameron writes to Ethiopian PM on behalf of British political dissident on death row


Andargachew “Andy” Tsege, a critic of the Ethiopian regime, was kidnapped in Yemen


(The Independent) – The Prime Minister has personally intervened in the case of a British father-of-three facing the death sentence in Ethiopia, after the man’s children appealed for his help.


David Cameron wrote to the Ethiopian Prime Minister in a bid to save the life of Andargachew “Andy” Tsege, 59, whose plight was revealed by The Independent last Friday.


His actions were in response to what he described as “very touching messages” from Mr Tsege’s children, who are calling for the Prime Minister to help get their father home.


Mr Tsege, who came to Britain as a political refugee in 1979, was arrested at an airport in Yemen in June and promptly vanished. Two weeks later it emerged he had been sent to Ethiopia, where he has been imprisoned ever since. The Briton, a prominent opponent of the Ethiopian regime, is facing a death sentence imposed five years ago at a trial held in his absence.


Menabe, his seven-year-old daughter, recently wrote to Mr Cameron asking him to help get her “kind, loving and caring dad” out of prison. Her twin brother, seven-year-old Yilak, simply asked: “What are you doing to get my dad out of jail?” Mr Tsege’s 15-year-old daughter, Helawit, summed up the mood of the family in her letter: “Please, please, please (!) bring him back soon. We miss him so much.”


Responding to the children’s appeals, the Prime Minister claimed the government is taking the case “very seriously”. In the letter to Yemi Hailemariam, Mr Tsege’s partner and mother of their children, Mr Cameron admitted “Ethiopian authorities have resisted pressure” from British officials to have regular “access” to Mr Tsege.


“As a result of the lack of progress to date I have now written personally to Prime Minister Hailemariam Desalegn to request regular consular access and his assurance that the death penalty (which the British Government opposes in all circumstances) will not be imposed,” he added. “I very much hope that there will be further progress to report in response to my letter,” he concluded.


Responding to the news yesterday, Maya Foa, head of the death penalty team at legal charity Reprieve, commented: “The Prime Minister says he is ‘concerned’ – but where is the outrage at this flagrant breach of international law, and the ongoing abuse of a British citizen?”


She added: “Andy’s small children are terrified of losing their father, his partner is desperate with worry, and we are no closer to seeing Andy released and returned to safety. Enough delays – we need firm action now to bring him home to London.”


Reprieve has begun legal moves which could result in a judicial review to force Foreign Office officials to press for Mr Tsege’s immediate release and return to Britain – something which the Government has resisted to date. A letter to Treasury Solicitors, sent last week by lawyers acting for the charity, argues: “Far from not being ‘entitled’ to request his return, the UK Government has every reason to do so and we urge you to exercise that power as a matter of urgency.”


Meanwhile, Mr Tsege’s family remain in limbo. The past four months have been “agonising” said Ms Hailemariam. “Waking up every day not knowing where Andy is or how he’s being treated is taking a terrible toll on my children and myself.” She added: “The Prime Minister has told our family that he is taking action, but it seems like next to nothing is being done to get Andy back. The children and I need him here with us in London. The Government must demand his return, before it’s too late.”

በቂሊንጦ ማረሜያ ቤት የማረሜያ ቤቱ ሀላፊዎችና የደህንነት አካላቶች ቅዱሳን መፃሀፎችንና የታራሚዎች የፍርድ ቤት ማስታወሻዎችን ማቃጠላቸው ታወቀ ::



ሰኞ እለተ ጥቅምት 10 2007 በቂሊንጦ ማረሜያ ቤት ቅዱሳን መፃሀፍትና የታራሚ ንብረት የሆኑ መፃሀፍቶችና የታራሚዎች የፍርድ ቤት ማስታወሻዎች ከሶስቱም ዝሆኖች ሰብስበው እንዲቃጠሉ መደረጋቸው ታወቀ።እነዚ መፃሀፎች በማረሜያ ቤቱ ሳንሱር ተደርገውና አልፈው የሚገቡ መፃሀፎች ሲሆኑ በሶስቱም የማረሜያ ቤቱ ዞኖች ቤተ መፃሀፍት ይገኛል።ይሁን እንጂ በየዞኖቹ በታራሚዎች እጅ የሚገኙትን የእምነት መፃሀፍትና ቅዱሳን መፃሀፍትና የታራሚዎች የግል ማስታወሻዎች እንዲቃጠሉ በማድረግ የማረሜያ ቤቶቹ አስተዳደሮች አቻ የሌለው እኩይ ተግባራቸውን ፍፅመዋል።

ይህ የማረሜያ ቤት ኢ ህገ መንግስታዊ ድርጊት የማረሜያ ቤቱ አስተዳደሮች በራሳቸው ፍቃድ የሚያከነውኑት ሳይሆን መንግስት ሆን ብሎ በነሱ በኩል የሚያስፈፅመው ኡክይ ተግባር መሆኑ በግልፅ ያሳያል ለዚህም ማሳያ ባሳለፍነው የተከበረው የረመዳን ወር መንግስት በንፁሀን ኢትዬዺያወያን ሙስሊሞች ላይ የአይሁድ ተልኮን ለማሳካት በወሰደው መንግስታዊ ሽብር (ጥቁር ሽብር)እለት ብዙ እስላማዊ መገለጫ የሆኑ ሂጃቦች ኮፊያና የመሳሰሉ የእምነት መገለጫ የሆኑ ነገሮች መቃጠላቸው የሚታወስ ነው አልፎም በርካታ ምእመናንን ለአካል ጉዳት የዳርገ አረመኔያዊ ድርጊት በመንግስት ታጣቂ ሀይሎች የተፈፀመ ሲሆን ከሁሉ በላይ የምእመናኑን ስነ ልቦና የነካና ፍፁም ከአእምሮ ሊፋቅ የማይችል ታላቅና ዘግናኝ ኢ ህገ መንግስታዊ የሆነ ተግባር. የሆነና የሀይማኖቱን ተከታዬች ፍፁም ያስቀየመ እንዲሁም የዚህን ስራአት ሸፍጠኝነት በጉልህ ያሳየ ተግባር ፍፅመዋል።

ይህ ሙስሊሞች የተፈጠሩለትን አላማ ያነገበውንና ለሰው ልጆች ሁሉ መመሬያ ሆኖ የተወረደውን የተከበረው ያአላህ ቃል የሆነውን "ቁርአን" ማቃጠላቸው ይታወሳል ።በሳለፍነው ሳምንትም በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራኔዬ በተለምዶ ዘነብ ወርቅ አካባቢ እንዲሁ ቁርአንና መፃሀፍ ቅዱስ ገንዳ ስር ተጥሎ መገኘታቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህ ሁሉ እምነት ላይ ያነጣጠሩ ዘመቻዎች በህዋት መረሹና እምነት የለሹ እምነቱን አቢዬቶ አድርጎ በሚገዛው የኢሀዲግ መንግስት ተጠናክሮ ቀጥሎዋል።

ሰሞኑን በቂሊንጦ ማረሜያ ቤት ቅዱስ መፃሀፍትን በማቃጠል የተደረገው ኢ ህገመንግስታዊ ድርጊት ታራሚዎችን ከአካልም ባለፈ በስነ ልቦናም ጫና ለማሳደርና ታራሚዎች በቂ የሆነ እውቀት እንዳይኖራቸው ሆን ተብሎ ታስቦ የተደረገ አረመኔያዊ የሆነ መንግስታዊ ሽብር ነው።ይሄ ደሞ አንድ ሀገርን አስከብራለሁ የዜጎችንና የሀይሞኖትን ነፃነት አስከብሪያለሁ ከሚል መንግስት የሚጠበቅ ተግባር. ባይሆንም ህዝቦቹን በማሰቃየት የመንፍስ እርካታ የሚያገኝው እንዲሁም የዜጎችን መሰረታዊ መቶች በመጣስ ወደር የሌለው የዚህ ስራአት ባለ ቤት የሆነው ህዋት መራሹ የወያኔ መንግስት ኢሀዲግ በማን አለብኝነት ስሜት እየፈፀመው ይገኛል. ታዲያ እነዚህ አካላት ዝም ሊባሉ አይገባም ሁሉም ነገር ይታለፋል ነገር ግን የሰው ልጅ የተፈጠረበትን አላማ ለመንጠቅ የሚደረግ ሙከራና ተግባር ሊቆም ይገባል ልብ ያለው ልብ ይበል!!!!

ቢቢኤን ሀሙስ ጥቅም 12 2007

Wednesday, October 22, 2014

FinFisher spyware seen targeting victims in Vietnam, Ethiopia RELATED

New research suggests a controversial spyware suite called FinFisher is being used to track activists in more countries than previously thought, including Vietnam and Ethiopia

Data integration is often underestimated and poorly implemented, taking time and resources. Yet itLEARN MORE

FinFisher, made by a subsidiary of U.K-based Gamma Group, is a set of remote intrusion and interception tools intended for use by law enforcement and intelligence agencies. But critics say the software is also used by repressive regimes to target activists, and they consider it malicious software.

Despite being known for several years, researchers say FinFisher's use is widening and that technical modifications are being made to help it evade detection.MORE ON NETWORK WORLD: 15 more useful Cisco sites

The latest research was published Wednesday by the Munk School of Global Affairs, part of the University of Toronto. Researchers there found more command-and-control servers used by FinFisher to control the software and collect captured information.

One sample of FinFisher, which the researchers dubbed FinSpy, appears to have been used to target an opposition group in Ethiopia called Ginbot 7, which was designated as a terrorist group by the country in 2011, wrote Morgan Marquis-Boire, a security researcher and technical advisor at the Munk School and a security engineer at Google.

FinSpy presented itself as an image file of Ginbot 7 in an attempt to get victims to open it, he wrote. It communicates with a command-and-control server, which is still operational, hosted on an IP address belonging to Ethiopia's state-owned telecommunications company, Ethio Telecom. The sample is similar to one that was sent to Bahraini activists in 2012.

"The existence of a FinSpy sample that contains Ethiopia-specific imagery and that communicates with a still-active command and control server in Ethiopia strongly suggests that the Ethiopian Government is using FinSpy," Marquis-Boire wrote.

A FinFisher product for Android mobile devices was also analyzed that communicated with a command-and-control server in Vietnam.

The software, called FinSpy Mobile for Android, sends a person's text messages to a Vietnamese phone number, Marquis-Boire wrote. The FinFisher suite of products includes similar software designed for iOS, Android, Windows Mobile and BlackBerry, including functions such as the ability to send GPS coordinates and snoop on conversations near where a phone is used.


"Both the command and control server IP and the phone number used for text-message exfiltration are in Vietnam, which indicates a domestic campaign," Marquis-Boire wrote. "This apparent FinSpy deployment in Vietnam is troubling in the context of recent threats against online free expression and activism."

A scan of the Internet also found 30 new command-and-control servers used to control FinFisher products in some 19 countries. Seven of the countries had not been known to host FinFisher servers before; they are Canada, Bangladesh, India, Malaysia, Serbia, Vietnam and Mexico. The report notes that those countries may not be involved in the actual surveillance, but networks located in those countries are being used to store information.

The Munk School has been monitoring FinFisher command-and-control servers since last year, but found in October that their methods for identifying those servers, called "fingerprinting," were no longer working, indicating FinFisher had been modified.

"We believe that Gamma either independently changed the FinSpy protocol or was able to determine key elements of our fingerprint, although it has never been publicly revealed," Marquis-Boire wrote.

Gamma Group and the subsidiary that makes the software, Gamma International, did not immediately respond to an email seeking comment.

Marquis-Boire wrote that the proliferation of FinFisher points to a larger issue with software and tools that are intended for legal surveillance but are abused by countries with poor human rights records. "This is indicative of a global trend towards the acquisition of offensive cyber capabilities by non-democratic regimes from commercial Western companies," he wrote.
On Tuesday, Reporters Without Borders named Gamma International as one of five companies whose products are believed to be used for spying on journalists and dissidents. It called on countries to implement stronger export controls around surveillance tools...

New research finds the surveillance spyware is spreading but may be used to spy on activists

የእንግሊዝ መንግሥት ለኢትዮጵያ ያዘጋጀውን የደኅንነት ማኔጅመንት ፈንድ አቋረጠ





በእንግሊዝ መንግሥት ገንዘብ ለኢትዮጵያ የደኅንነት ኃላፊዎች ይሰጥ የነበረው የደኅንነት ማኔጅመንት ፕሮግራም ተቋረጠ:ሪፕሪቭ የተባለ ነፃ የሕግ አገልግሎት የሚሰጥ የእንግሊዝ ኩባንያና ሌሎች የሰብዓዊ መብት አቀንቃኞች፣ ካለፈው ዓመት አጋማሽ ጀምሮ የእንግሊዝ መንግሥት ይህንን ፕሮግራም እንዲያቋርጥ ግፊት ሲያደርጉ ነበር::

እነዚህ ወገኖች ይህንን ግፊት የጀመሩት የኢትዮጵያ መንግሥት በልማት ምክንያት ዜጐችን ከመኖሪያ አካባቢያቸው ያፈናቅላል በሚል ክስ ነበር:: ይሁን እንጂ የግንቦት ሰባት ጸሐፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመንና
በኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይሎች፣ ባለፈው ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ኤርትራ ለመጓዝ የመን በኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይሎች፣ ባለፈው ሐምሌ 1ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ኤርትራ ለመጓዝ የመንሰንአ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር ውለው ወዲያውኑ ለኢትዮጵያ መንግሥት ከተላለፉ በኋላ፣ በእንግሊዝ መንግሥት ላይ ጫናው እንዲጠናከር ሲጥሩ ነበር::
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት በኃይልም ሆነ በተገኘው አማራጭ ለመለወጥ የሚታገለው የግንቦት ሰባት አመራር ይሁኑ እንጂ፣ ዜግነታቸው እንግሊዛዊ መሆኑ ተጨማሪ ግፊት ይፈጥራል ብለውም ነበር::
እሳቸው በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ በእንግሊዝ መንግሥት ላይም ሆነ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ከፍተኛ ግፊት ከሚያደርጉት መካከል፣ መቀመጫውን ለንደን ያደረገው ነፃ የሕግ አገልግሎት የሚሰጠው ተቋም የሆነው ሪፕሪቭና የአውሮፓ ኅብረት የሰብዓዊ መብት ኮሚቴ ይገኙበታል::
የሪፕሪቭ የሕግ ዳይሬክተር ቲኔክ ሀሪስ በነሐሴ ወር ለእንግሊዝ መንግሥት ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ጀስቲገን ግሪንግ በጻፉት ደብዳቤ፣ ‹‹የእንግሊዝ ዜግነት ያለውን ግለሰብ ላገተውና ቶርቸር በማድረግ ለሚጠረጠረው የኢትዮጵያ መንግሥት ኃላፊዎች ይህንን ፕሮግራም መስጠት ተገቢ ነው ወይ? ተገቢ ነው ብለው ካላመኑ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እስካልተፈቱ ድረስ ምን ዕርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ቢያሳውቁን?›› በማለት ጥያቄ አቅርበው ነበር::
የአውሮፓ ኅብረት የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ኮሚቴ ባለፈው መስከረም ወር ባካሄደው ጉባዔው በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እስር ላይ የእንግሊዝ መንግሥት ምንም ዓይነት ጫና አለማሳደሩን በመውቀስ አስፈላጊ ነው የተባለ ውሳኔ በኢትዮጵያ ላይ ለማሳለፍ የሁለት ወራት ጊዜ ቀጠሮ ወስዶ መበታተኑን መዘገባችን ይታወሳል::
ይህ ጫና ባለበት በአሁኑ ወቅት የእንግሊዝ መንግሥት ዲፓርትመንት ፎር ኢንተርናሽናል ዴቨሎፕመንት (ዲኤፍአይዲ) ለኢትዮጵያ የደኅንነት ኃላፊዎች ይሰጥ የነበረውን የደኅንነት ማኔጅመንት ፕሮግራም አቋርጧል::
ፕሮግራሙ የተመረጡ የኢትዮጵያ የደኅንነት ኃላፊዎች በእንግሊዝ አገር በደኅንነት ማኔጅመንት የማስትሬት ዲግሪያቸውን እንዲሠሩ የሚያግዝ ነበር::
የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጪ ወደ 70 ሚሊዮን ፓውንድ ሲሆን፣ ለመጀመሪያው ዙር ፕሮግራም ሁለት ሚሊዮን ፓውንድ ያስፈልግ ነበር::
ለዚህ ዓመት ተይዞ የነበረው የሁለት ሚሊዮን ፓውንድ ወጪ ለአጠቃላይ ፕሮግራሙ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ::
የዲኤፍአይዲ የኢትዮጵያ ቢሮ ጉዳዩን በተመለከተ ከሪፖርተር በኢሜይል ለቀረበለት ጥያቄ ፕሮግራሙ መቋረጡን አረጋግጧል:: ነገር ግን ምክንያቱ ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር ግንኙነት እንደሌለው አስታውቋል::
‹‹ፕሮግራሙ የተቋረጠው የእንግሊዝ መንግሥት ለፕሮግራሙ የሚያወጣውና የሚያገኘው ምላሽ (ኢንቨስትመንት ሪተርን) የሚጣጣሙ ባለመሆናቸው ነው፤›› በማለት በደፈናው መልሷል::

ሪፖርተር

Sunday, October 19, 2014

የቀድሞው የኢሕአዴግ ባለስልጣን አቶ ኤርሚያስ ለገሰ “ኢሕአዴግ በምርጫ ስልጣኑን ያስረክባል የሚል እምነት የለኝም” አሉ

የቀድሞው በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ስለ ቀጣዩ የኢትዮጵያ ምርጫ፣ ስለ ምርጫ 97ቱ ግድያ ፣ ስለ አገዛዙ ያልተሳካ የዲያስፖራ ፖሊሲ ፣የሕወሃት ኢትዮጵያን እያተራመሰ ረጅም ጊዜ ስልጣን ላይ ለመቆየት ማሰቡን ከውስ ተመልካች አንጻር ፈትሸውታል። ስለ ቀጣዩ መጽሐፋቸው መጠነኛ ፍንጭ ሰጥተዋል።
ከአቶ ኤርሚያስ ለገሰ ጋር በቬጋስ የኢትዮጵያ ራዕይ ማህበር በጠራውና የታሰሩና የተሰደዱ ጋዜጠኞችንና የፖለቲካ እስረኞችን ለመርዳት በተጠራው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ ሕብር ራድዮ አግኝቶ አነጋግሯቸዋል። ሙሉውን ቃለ መጠይቅ ተከታተሉ።



Friday, October 17, 2014

በተቃዋሚዎች የሚረጨውን መርዝ ለማርከስ ለዩኒቨርስቲ ምሁራንን ለሌሎች ዜጎች የውይይት መድረኮች መዘጋጀታቸውን አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ

99 በመቶ በላይ የኢህአዴግ አባላት በሞሉበት ፓርላማ ውስጥ ብቸኛ የሆኑት የአንድነት ፓርቲ ተመራጩ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በቅርቡ መንግስት ለዩኒቨርስቲ መምህራን፣ ተማሪዎችና የመንግስት ሰራተኞች የሚሰጠውን የፖለቲካ ስልጠና አስመልክቶ ላቀረቡት ጥያቄ መልስ የሰጡት ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ውይይቱን ማድረግ ያስፈለገው ትምክህተኞች፣ ጸረ ሰላም ሃይሎችና ጠባቦች የሚረጩት መርዝ ትክክል አለመሆኑን ለማሳየት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ውስጥ የመንግስት ባለስልጣናትና ተቃዋሚዎች ኢህአዴግን በመጥላታቸው በብሄሮች መካከል መቃቃር እና ግጭቶች እንዲፈጠሩ እየሰሩ በመሆኑ መንግስት በሁለቱም ላይ እርምጃ ይወስዳል ብለዋል።በጋምቤላ በመዠንገር አካባቢ የተከሰተው ግጭት በመንግስት ባለስልጣናትና በተቃዋሚዎች የተፈጠረ መሆኑን፣ እጃቸው አለበት የተባሉ የመንግስት ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ጠ/ሚ ተናግረዋል።

የጠ/ሚንስትሩ ንግግር ኢህአዴግ በየቀኑ እርሱ በሚቆጣጠራቸው የመገናኛ ብዙሃን የሚያሰራጨው ፕሮፓጋንዳ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ማጣቱ እንዳሳሰበው፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚታየው አለመረጋጋት እየጨመረ መምጣቱን ለማመን መገደዱን ያሳየነ ነው ሲል በስፍራው የተገኘው ዘጋቢያችን ገልጿል።

አቶ ግርማ ሰይፉ መንግስት በአምስት አመታት ውስጥ ያቀደውን እቅድ ከፕሮፓጋንዳ ባለፈ በበቂ ሁኔታ ሊሰራ አለመቻሉን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማንሳት ጠይቀዋል።የባቡር መንገድ ከ100 ኪሜትሮች በላይ አለመሰራቱ፣ ይህን ድክመት ለመሸፈንም በአዲስ አበባ ያለውን የባቡር መንግድ ደጋግሞ በማሳየት ድክ መትን ለመሸፈን ሙከራ መደረጉን አቶ ግርማ ገልጸዋል።

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ የባቡር ፐሮጀክቶች በብድር የሚሰሩ በመሆኑን በአንዳንድ ፕሮጀክቶች ላይ ብድር ለማግኘት ችግር መኖሩን በመጠቆም ትኩረቱ ከአዲስ አበባ ጅቡቲና ከመቀሌ አዋሽ ባሉት የባቡር ፕሮጀክቶች ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ይሁን እንጅ እነዚህም ፕሮጀክቶች ከጅምር ያለፉ አለመሆኑን ከንግግራቸው ለመረዳት ተችሎአል።

70 በመቶ የስኳር ፋብሪካዎች በዚህ አመት እንደሚጠናቀቁና ስኳር በማምረት ወደ ውጭ መላክ እንደሚጀመር ጠ/ሚ ቢናገሩም፣ በመላ አገሪቱ ስኳር በመጥፋቱ ሻሂ ቤቶች ስኳር በኮታ ለመውሰድ እየተገደዱ፣ ሌሎች ተጠቃሚዎች በቂ ስኳር ለማግኘት በማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸውን ዘጋቢያችን ገልጿል።

ጋዜጠኞች እየታሰሩ፣ የውይይት ምህዳሩ እየጠበበ መምጣቱን የገለጹት አቶ ግርማ፣ መንግስት ከጦር ይልቅ ሃሳብንና ውይይትን እንደሚፈራ ያሳያል ብለዋል። አቶ ሃይለማርያም ጋዜጠኞች ህዝብን ከህዝብ ለማጋሸትና ሽብር ለመፈጸም በመንቀሳቀሳቸው መታሰራቸውን በመግለጽ የአቶ ግርማን አስተያየት ውድቅ አድርገዋል።


ናይሮቢ የሚገኘውን የጋዜጠኛ ሚሊዩን ሹሩቤ አስከሬን ወያኔ ወሰደው።





የጋዜጠኞች ፕሬዝዳንት ነኝ ብሎ ራሱን የሰየመው አንተነህ አብርሃም ለጋዜጠኞች እየደወለ እየዛተ ነው፡፡

በቅርቡ የስደቱን አለም የተቀላቀለው እና ባጋጠመው የምግብ መመረዝ ድንገት ከዚህ አለም በሞት የተለየው የማራኪ መጽሄት ማኔጂንግ ዳይሪክተር እና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ አስከሬን ወያኔ በጉልበት መውሰዱን ከናይሮቢ ተሰምቷል።

በወያኒ ሴራ በተመረዘ ምግብ ሞቷል የሚባለው እና ለሞቱን መንስኤ እንደሆነች የምትጠረጠረው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማት ባልቤት የሆነች ግለሰብ ራሷን የሰወረች መሆኑ ሲታወቅ ጋዚጠኛ ሚሊዮንን ከዚመሞቱ ቀድሞ በየምሽቱ እየመጣች በዘመናዊ መኪና ፒክ እያደረገቸው ስታዝናናው እንደነበር ይታወቃል።የሚሊዮን ሹሩቤን አስከሬን ወደ ሃገር ቤት ለመላክ ሲሰሩ የነበሩ ስደተኛ ጋዜጠኞች ፕሮሰስ ሲያደርጉበት የነበረውን ዶክመንት አስረክበዋል፡፡ የጋዜጠኞች ፕሬዝዳንት ነኝ ብሎ ራሱን የሰየመው አንተነህ አብርሃም ለጋዜጠኞች እየደወለ እየዛተ ነው፡፡

መንግስት ጋዜጠኞችን አላሰደድኩም በማለት የጀመረውን ድራማ በአሳዛኝ ሁኔታ አስክሬን ቁጭ ብለው የሚጠብቁት ቤተሰብ ላይ ድራማ መስራት ስለጀመረና አስከሬኑን ወደ ሃገር ቤት ለመላክ እየሰራ ያለን ጋዜጠኞች ለደህንነታችን አስጊ ሁኔታ በመፈጠሩ ካሁን በኋላ የጋዜጠኛ ሚሊዮን አስክሬን መላክ ጉዳይ ከእኛ ቁጥጥር ውጭ መሆኑን ሃገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ያላችሁ የስራ ባልደረቦቻችን እንዲሁም መላው ህዝብ እንድታውቁት ይሁን ፡፡ ከቤተሰብ ተወክለው መጡ የተባሉት ሰዎች የማናውቃቸው ሲሆን አስከሬኑን ለመውሰድ ሀገር ውስጥ ገብታለች የተባለችው የጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹሩቤ እህት የት እንዳለች የማናውቅና እህቱንም ማን እንደተቀበላት የምናውቀው ነገር አለመኖሩን ማሳወቅ እንፈልጋለን ፡፡የሚሊዮን ሹሩቤን ሞት ተከትሎ በኪንይ የምግኙ ስደተኛ ጋዜጠኞች በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እና ክትትል ስር መግባታቸው ታውቋል።


Thursday, October 16, 2014

የወያኔ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሐኖም ለጥቂ ተሳቱ


ሀፍረትና ይሉኝታ የሚባሉ ነገሮች በአጠገባቸው ያለ የማይመስላቸው ብልግና ጭካኔ ወገንን ካለ ህግ መግደል ማዋረድ የህዝብ ሀብት በጠራራ ፀሐይ መዝረፍ ለሰው የተስጠ ፀጋ አድርገው የሚቆጥሩትን የወያኔ መንግስት በሔደበት ቦታ ሁሉ መዋረድ ማየትና መስማት የተለመደ ሆኖአል።

በዛሬው አለት በኖርዌ Invest in Ethiopia ተብሎ በ Norwegian-African Business Association አዘጋጅነት በተጠራው ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ ወደ ኖርዌ የመጣውን የወያኔ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሐኖም ላይ Human right before investment አና የተለያዩ መፈክሮች በማሠማትና የእንቁላል ናዳ በማውረድ የሚንስትሩን አንገት በማስደፋት የኖርጂያንን ፖሊስ አጨናንቀውት ውልዋል

የዚህ የወረበላ የወያኔ መንግስት መውደቂያ አሁን ነው በዘር በሐይማኖት መከፋፈል ያክትማል እጅ ለ እጅ ተያይዘን የነፃነት ዜማ አናዜማለን ኢትዮጵያ የብሔር ቢሔረስቦች አገር እንጂ ያአንድ ብሔር አይደለችም በማለት የተቃውሞ ስልፉን በተሳካ ሁሄታ አጠናቋል http://www.nrk.no/nyheter/1.11989821

Ethiopian journalist Died in Exile


A prominent Ethiopian journalist, Million Shurube, died in Nairobi, Kenya, where he had been in exile since September 2014.

Million, father of a son, passed away on 13, October 2014 at Kenyata hospital at the age of 33. The cause of his death is still unclear.

Million was one of a dozen of Ethiopian journalists forced in to exile recently having been harassed, threatened, accused, and charged with fabricated terrorism offenses. He fled from Ethiopia on September 2014 to escape from imprisonment.

Affectionately known as “Milli”, Million Shurube served as a journalist for more than 10 years. He was the founder and managing editor of a weekly magazine “Maraki”, and had worked for different publications including the now-defunct Abay, Ethiop, and Google newspapers.

Million was also the author of a book discussing the deep rooted social problems in Ethiopia.

Reports indicate that the journalist got sick 20 days after he left his country, and finally died having suffered for more than 15 days. Some weeks ago, he was told to have got Taifoid at a clinic and used to receive medical treatment.

“Starting from September 24, he was not feeling healthy; he had headache”, his room partner said yesterday in her commentary on his death.

“Recalling memories of his son and his country, he used to cry. So that we would advice him to not be worried too much believing stress was the cause to his headache. But, we later took him to a nearby clinic when we saw no improvement in his health and he was given medication”, she explained.

According to sources, the health of the journalist got much worst over the past weekend. Fallen unconscious he was taken to Kenyata hospital on 11 October midnight and died after two days.

Million was known for his exciting writings on issues including art, religion, and tradition. He was also known for his out spoken and inspiring articles on the political and human right crisis in Ethiopia.

Plight of Ethiopian Journalists

Ethiopia is one of the leading repressive nations in Africa. With at least 17 journalists in jail, the country is now the second leading jailer of journalists and bloggers in the continent.

Despite the growing condemnation from the west, the country has continued to intensify its crackdown on the private press aiming to silence independent voices ahead of the 2015 national election. In the past few months only, more than 9 publications have been closed, of them 1 newspaper and 5 magazines were shutdown having faced fabricated accusations and charges.

The country has also sentenced 3 publishers in abstain to more than three years in prison few weeks ago. All of the journalists were convicted on charges of “inciting violent revolts, printing and distributing unfounded rumours, and conspiring to unlawfully abolish the constitutional system of the country.”

In other latest case, the Federal High Court in the capital Addis Ababa also convicted the prominent journalist Temesghen Desalegn. Early this year, a group of vibrant bloggers along with 3 other journalists had been arrested on charges of “terrorism” offenses. A journalist association called Ethiopian Journalists Forum (EJF) was also being accused and later banned, and many of its leaders were eventually forced to flee the country.

As the crackdown continues to intensify, the number of journalists fleeing Ethiopia is rising dramatically. According to recent reports, in recent months only more than 25 journalists and bloggers have fled the country in order to escape from imprisonment. In the face of complicated problems, many of them are currently struggling to survive. The death of Million highlights the plight of these journalists.

By: BetreYacob

Wednesday, October 15, 2014

Open letter to U.S. President Barack Obama



By Abebe Gellaw
Note: Upon the invitation of the Democratic National Committee, I had another opportunity to attend an exlusive event with President Obama. He spoke about the opportunities and challenges that his administration is taking up at home and abroad. In the October 10 event held at The W Hotel in downtown San Francisco, I took the golden opportunity to hand the following letter to a White House aide, who promised to deliver it to the President. In any case, here it is in a form of an open letter to President Obama.
….
President Barack Obama
1600 Pennsylvania Ave NW,
Washington, DC 20500
Mr. President,
First and foremost, I would like to express my sincere appreciation to you for taking some bold steps to inspire the future leaders of Africa. The Mandela Washington Fellowship, which aims to bring 500 bright and visionary young African leaders to the White House and Capitol Hill annually for a unique experience and learning, is arguably one of the best initiatives that the government of the United States has ever taken.
I am sure many Africans support such an initiative because the future and hope of the African continent hinges upon new breed of visionary leaders that are willing to boldly take risks to lead Africa out of the darkness of brutal tyranny and corruption into the sunshine of freedom, dignity, justice and democracy. Some of these young dreamers and visionaries you are trying to inspire will certainly follow the footsteps of Martin Luther King Jr., Gandhi and Mandela.
If African nations suffering under tyrannies are to get out of the quagmire of abject poverty, ignorance, corruption, abuse of power and the indignity they are suffering at the hands of its own rulers, a new breed of African leaders with selfless mindsets have to take the lead. However, we should also remember that countless young visionary Africans who could have joined the coveted fellowship cannot even apply because most are thrown in harsh jails, some are killed and many are tortured and abused because of their views and the beautiful dreams they cherish.
Mr. President, it would be disingenuous of me if I am remiss to raise the serious concerns that freedom fighters and activists like myself are expressing in the aftermath of the African Leadership Summit that you hosted last August. While the summit should be applauded as the first ever U.S.-Africa summit aimed at engaging African rulers, the list of guests was truly disturbing.
Just to mention a few among many, Teodoro Obiang of Equatorial Guinea, Gambia’s Yahya Jammeh, Cameroon’s Paul Biya, Jose Eduardo dos Santos of Angola even Ethiopia’s Hailemariam Desalegn, who is the front man for TPLF’s brutal regime, are among the worst human rights abusers in the continent that are shedding the blood of so many innocent people and terrorizing their own people to sustain their tyranny and corruption. Africa’s biggest obstacles to progress and change are its own abusive rulers. Without respect for human rights, progress and development has little meaning because it is not the aspiration of any nation to starve and die dispossessed of dignity in silence and fear.
Mr. President, it is true that some African countries are registering some progress. But in so many countries like Ethiopia, where crony capitalism is on the rise, the hyped up progress and development is driven by a greedy ethnocentric ruling elite. As you very well know, crony capitalism mainly benefits the privileged few at the detriment of the majority.
Mr. President, during your meeting with a delegation of Ethiopian officials that included Prime Minister Hailemariam Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom last month at the United Nations, you said: “Obviously we’ve been talking a lot about terrorism and the focus has been on ISIL, but in Somalia, we’ve seen al-Shabaab, an affiliate of al Qaeda, wreak havoc throughout that country. That’s an area where the cooperation and leadership on the part of Ethiopia is making a difference as we speak. And we want to thank them for that.” It is indeed a great honor for Ethiopia to get your administration’s commendation for its role in the global war on terror.
However, any careful reading of the annual State Department report on human rights reveals disturbing facts that maybe unintentionally overlooked. It is clear that the greatest threats on the safety and security of the ordinary people of Ethiopia do not come from al Qaeda or al-Shabaab. It comes from the very people who sat with you pretending to be committed to be fighting against terrorism. As a matter of fact, after the fall of the brutal military rule of Mengistu Hailemariam in 1991, it is a tragedy that another tyranny is under the TPLF is terrorizing Ethiopia for over two decades.
The TPLF regime has killed, maimed, tortured and jailed countless Ethiopians during its reign of terror. So many journalists, bloggers, activists, dissidents and freedom fighters are being jailed and tortured accused of fictitious terrorism charges. The award winning journalists Ekinder Nega, Reeyot Alemu, Wubishet Taye, the young Zone9 bloggers, leaders of Muslim rights movement, activists and dissidents like Andargachew Tsege, Andualema Arage, Bekele Gerba, Olbana Lelisa and countless others have been labeled terrorists. They are languishing in rat-infested jails abused, tortured and brutalized. Such a cowardly attack against innocent civilians for speaking out against tyranny is nothing but terrorism.
President Obama, please allow me to quote just two paragraph from the 2013 U.S. State Department Human Rights Report on Ethiopia: “The most significant human rights problems included: restrictions on freedom of expression and association, including through arrests; detention; politically motivated trials; harassment; and intimidation of opposition members and journalists, as well as continued restrictions on print media. On August 8, during Eid al-Fitr celebrations, security forces temporarily detained more than one thousand persons in Addis Ababa. The government continued restrictions on activities of civil society and nongovernmental organizations (NGOs) imposed by the Charities and Societies Proclamation (the CSO law).”
“Other human rights problems included arbitrary killings; allegations of torture, beating, abuse, and mistreatment of detainees by security forces;reports of harsh and, at times, life-threatening prison conditions; arbitrary arrest and detention; detention without charge and lengthy pretrial detention; a weak, overburdened judiciary subject to political influence; infringement on citizens’ privacy rights, including illegal searches; allegations of abuses in the implementation of the government’s “villagization” program; restrictions on academic freedom; restrictions on freedom of assembly, association, and movement; alleged interference in religious affairs; limits on citizens’ ability to change their government; police, administrative, and judicial corruption; violence and societal discrimination against women and abuse of children; female genital mutilation/cutting (FGM/C); trafficking in persons; societal discrimination against persons with disabilities; clashes between ethnic minorities; discrimination against persons based on their sexual orientation and against persons with HIV/AIDS; limits on worker rights; forced labor; and child labor, including forced child labor. Impunity was a problem. The government, with some reported exceptions, usually did not take steps to prosecute or otherwise punish officials who committed abuses other than corruption.”
Mr. President, I hope you agree with me that the disturbing testimony from the State Department is as bleak as a CIA report on al-Qaeda. It should be noted here that the Tigray People’s Liberation Front was also blacklisted in the Global Terrorism Database of the U.S. Department of Homeland Security before it came to power. Terrorist groups, whether they operate as a government or a band of pirates, have similar objectives and aspirations. They try to cause great fear and impose their will upon others through killings, massacres, tortures, kidnappings and all sort of inhuman tactics.
In the aftermath of the 2005 brutal crackdown, U.S. Senator Patrick Leahy had said, in a statement, “Ethiopia has been an ally of the United States in combating international terrorism, yet it is using similar tactics against its own people…The government’s heavy handed tactics to steal the election and persecute those who sought to play by the rules of democracy, should be universally condemned.”
Mr. President, so many Ethiopians appreciate your effort to help Ethiopia. But the United States should not provide unconditional funds to the tyrants in power that are terrorizing the oppressed people of Ethiopia. The United States should not also lose its unique place as the beacon of hope and freedom. It needs to live up to its core values and creeds. If the United States needs credible allies against terrorism, it has to look into the records of questionable allies and press them to clean their own house first before fighting other terrorists.
Mr. President, as you said: “We lose ourselves when we compromise the very ideals that we fight to defend. And we honor those ideals by upholding them not when it’s easy, but when it is hard.”
Ordinary people like me will continue to make every effort to stick out reminders and notes so that the government of the United States continues to uphold the foundational values and ideals that have made this country truly great and admirable. I do hope that eventually we will get noticed and our voices will be heard.
Most respectfully,

Abebe Gellaw

አልሸባብ በቦሌ አካባቢ የሽብር ጥቃት ሊቃጣ ይችላል – የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር




የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር የዲፕሎማሲ ደህንነት ክፍል ዛሬ ባወጣው አስቸኳይ መልዕክት በአዲስ አበባ የሚገኙ የአሜርካ ዜጎች ብዙ ሰዎች የተሰበሰቡባቸውን: ኢትዮጵያዊያንና የውጭ ዜጎች ከሚያዘወትሯቸው ቦታዎች እንዲርቁ አሳስቧል::

ኢንባሲው የደረሰው የአደጋ መረጃ አልሸባብ የቦሌን አካባቢ ለማጥቃት እንዳሰበ ይገልጻል:: በቦሌ አካባቢ የሚገኙ ምግብ ቤቶች: ሆቴሎች: ምሽት ቤቶች: የአምልኮ ቦታዎች: ትላልቅ የሸቀጥ ሱቆችና: ሞሎች የሽብር ሴራው ኢልማዎች ሊሆኑ ስለሚችሉ ዜጐች ከእነዚህን ተቋማት ሌላ ማሳሰቢያ እስከሚወጣ ድረስ ገለል እንዲሉም ያሳሰባል::

አደጋው ሊጣል የታሰበበት ትክክለኛ ቦታ በእርግጥ ስላልታወቀ የአሜሪካ ዜጎች ነቃ ብለው የግል ደህንነታቸውን እዲከታተሉም በመጨመር ያሳስባል::

ምንጭ:- OSAC

የዞን9 ጦማርያኑ እና የወዳጅ ጋዜጠኞች የፍርድ ቤት ውሎ



‪#‎FreeZone9bloggers‬ ‪#‎Ethiopia‬

ከሁለት ወር ቆይታ በኋላ በነሶልያና ሽመልስ የሽብር ወንጀል የክስ መዝገብ ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡት ስድስቱ የዞን9 ጦማርያን እና ሶስቱ ጋዜጠኞች ቀጠሮ ችሎቱ ከ20 ቀን በኃላ እንዲቀርቡ ተለዋጭ ቀጠሮ በመስጠት ተጠናቀቀ።


ፍርድ ቤቱ በዛሬው ውሎው የተከሳሽ ጠበቆች ክሱ ላይ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ አቃቤ ህግ አይቶ ምላሽ እንዲሰጥበት የተቀጠረ ሲሆን በዚያም መሰረት ለተከሳሽ ጠበቆች የክስ መቃወሚያ አቃቤ ህግ የፅሁፍ ምላሽ ሰጥቷል ።

ፍርድ ቤቱም የጠበቆችን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ መርምሮ በክሱ ሂደት ላይ ብይን ለመስጠት ለተጨማሪ ሃያ ቀን ለጥቅምት 25 ቀጠሮ ሰጥቷል።

በተጨማሪም የሴት ተከሳሾችን በጓደኛና በቤተሰብ አለመጎብኘት ተከትሎ ያቀረቡትን አቤቱታ እንዲያስረዳ የማረሚያ ቤቱ እንዲገኝ ጥሪ ቢደረግም አለመገኘቱን እና በፓሊስ በኩል ምላሽ ይዞ መቅረቡን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ በሚቀጥለው ቀጠሮ የማረሚያ ቤቱ ሃላፌ እንዲገኙ ትእዛዝ አስተላልፎ ነበር። ነገር ግን ሴት ተከሳሾች በተለይ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳየ የመጎብኘት መብት መሰረታዊ መብታቸው በመሆኑ 20 መቆየት እንደማይገባ በመጠየቃቸው ፍርድ ቤቱ የሴት ተከሳሾችን የጉብኝት መብት አስመልክቶ ለማየት ለጥቅምት 11 አጭር ቀጠሮ ሠጥቷል ።

በዛሬው እለት ነጭ በመልበስ የተገኙት ተከሳሾች በመልካም ፈገግታ እና በጠንካራ መንፈስ የነበሩ ሲሆን በፈገግታ ወዳጅ እና ጓደኞቻቸውን ሰላም ሲሉ ተስተውለዋል።

በመጨረሻም የሚቀጥለው ቀጠሮ ለጥቅምት 25 የተወሰነ ሲሆን የሴት ታሳሪዎችን የጉብኝት መብት ጥያቄ አስመልክቶ በጥቅምት 11 ችሎቱ ቀድሞ ይሰየማል ተብሎ ይጠበቃል።

የዞን9 ጦማርያን የክሱን ፈጠራነት፣ የጦማርያኑን እና ጋዜጠኞቹ በመአከላዊ ምርመራ ያለፉበትን የመብት ጥሰት እያስታወስን የፍትህ ስርአቱ የሚታማበትን የፓለቲካ መጠቀሚያነት ክስ ወዳጅ ጋዜጠኞችን እና ተከሳሽ ጦማርያንን በነፃ በማሰናበት ፍርድ ቤቱ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ እንደሚጠቀምበት ተስፋ እናደርጋለን።


Like

Tuesday, October 14, 2014

ተመስገን ደሳለኝንም አሰሩት


(ኢ.ኤም.ኤፍ) ታዋቂው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ታሰረ። ተመስገን ደሳለኝ ከትላንት ጀምሮ፤ የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶበት የታሰረ መሆኑን ለማወቅ ችለናል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከዚህ በፊት በተከሰሰበት እና ፍርድ ቤት ሲመላለስባቸው በነበሩት ክሶች ነው አሁን ለእስር የበቃው።



Temesegen Desalegn


ጋዜጠኛ ተመስገንን ለክስ ካበቁት ጽሁፎች መካከል፤ “መጅሊሱ፣ ሲኖዶሱና የአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ማጥመቂያዎች”፣ “የፈራ ይመለስ” እና “የብሄረሰቦች መብት እስከ መጨፈር” በሚል ርእስ የጻፋቸው ጽሁፎች ናቸው። ሁሉም ጽሁፎች አሁን እንዳይታተም በታገደው ፍትህ ጋዜጣ ላይ የወጡ ነበሩ። በነዚህ ጽሁፎች ምክንያት አቃቤ ህጉ የክሱን ጭብጥ የመሰረተው፤ መንግስትን በአመፅ ለመናድ ቀስቅሷል፣ የመንግስትን ስም አጥፍቷል፣ የህዝብን አስተሳሰብ አናውጧል፤ በሚል ሲሆን ጽሁፎቹም ሆኑ ክሱ ሁለት አመታትን አስቆጥሯል።


በእነዚህ ክሶች ምክንያት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድ ቤት በቀጠሮ ሲመላለስ ቆይቶ፤ ትላንትና ግን ፍርድ ቤቱ በተመስገን ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ አሳልፏል። በመሆኑም ጋዜጠኛ ተመስገን በ እስር ላይ ቆይቶ የቅጣት ውሳኔውን ከ2 ሳምንታት በኋላ ማለትም ጥቅምት 17፣ 2007 በፍርድ ቤት ተገኝቶ እንዲያዳምጥ ውሳኔ ተሰጥቷል። በመሆኑም ጥቅምት 17 ቀን ከታሰረበት መጥቶ፤ ለምን ያህል ተጨማሪ አመታት እንደሚታሰር በንባብ ተነግሮት ወደ ወህኒ እንዲወርድ ይደረጋል ማለት ነው።


በማጠቃላያችን ላይ አንድ ነገር ማከል ፈለግን። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከታሰረ በኋላ በቅርብ ምስክርነታቸውን ከሰጡት ውስጥ በፋክት መጽሄት ላይ አብሮት የሰራው ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ አንዱ ነው። የቴዎድሮስን ጽሁፍ ከዚህ ቀጥሎ በማቅረብ ዘገባችንን እናበቃለን።


ስለ ተመስገን ደሳለኝ (ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ)


(ቀደም ብዬ መፃፍ የነበረብኝ ሀሳብ)
ዛሬ ከደቂቃዎች በፊት የተመስገንን መታሰር ስሰማ አዘንኩ ። “በምንና እንዴት ታሰረ? መታሰሩ አግባብ ነው? ” የሚለውን አላነሳም ። ምክንያቱም ከግምት የተሻለ እውቀት የለኝም ። አሁንም በቀጠሮው ቀን ምን እንደሚል አላውቅም ። ይህ ሀሳቤም አሁን ተመስገን ካለበት ሁኔታ ጋር አይገናኝም ። ይሁንና ቀደም ሲል መፃፍ የነበረብኝን ሀሳብ ላንሳ ።
ተመስገን ፋክት መጽሔት ላይ እንድጽፍ ሲያነጋግረኝና ከዚያ በፊት ለእሱ የነበረኝ ግምት የተለያየ ነው ። አራት ኪሎ አግኝቼ ያናገርኩትና ፋክት እስክትቆም ያየሁት ተመስገን ለእኔ እንዲህ ነው ።
የሚጮህ ጽሁፍ የሚጽፈው ተመስገን በጣም ጸጥተኛ ነው ። ደፋሩን ጸሀፊ የትህትና ፍርሀት ያለበት ሆኖ ነው ያገኘሁት ። ለስላሳነቱ የውስጥ ባህሪው ነው ። ከሁሉም በላይ በግል እንደራሴም ይሁን እንደ ሙያውን ወዳድ ጋዜጠኛ ፍጹም ነጻነት የሰጠኝ ከሁሉም በላይ ተመስገን ደሳለኝ ነው ። አብረን ለመስራት ተስማምተን ስለጽሁፍ ይዘት ስናወራ “ምን አይነት ይዘት ያለው ጽሁፍ እንድጽፍ ነው የምትፈልገው?” ስለው የሰጠኝ መልስ መቼም የማልረሳውና በአንዱ የመጽሔቱ እትም ላይ የጻፍኩት ነው ። ” እንዲህ ጻፍ አልልህም ። የፈለከውን ጻፍ ። ኢህአዴግ በአለም ላይ ታይቶ የማይታው ዲሞክራሲ አምጥቷል ብለህ ካመንክ የመጻፍ መብት አለህ ። አንተ ስም ስላለህ ድጋፉንም ተቃውሞውንም የምትቀበለው ራስህ ነህ ” አለኝ ። ይህ ለአንድ ጋዜጠኛ ፍፁማዊ ነጻነት ነው ። ተመስገን ደሳለኝ ከጥሩ የብር ክፍያው ጎን ይህን ከፍሎኛል ። የትም ብሄድ ይህን ነጻነት አላገኘውም ። በፋክት መጽሔት ቆይታዬም ከቃለመጠይቅ ጀምሮ እስከ መጣጥፎች በዚህ ነጻነት ነው የሰራሁት ። አንድም ቀን በዚህ ርዕስ ላይ ብትፅፍ ያላለኝና በሀሳቤ ጣልቃ ያልገባ ሰው ይህ ሰው ነው ። መጻፍ ሲገባኝ ያልጻፍኩት ወይም ያልተገባ ሀሳብ ጽፌ ከተገኘሁ በራሴ ግፊትና ሀሳብ ነው ። ለጻፍኩት ሁሉ ሀላፊነቱን የምወስደው እኔ ብቻ ነኝ ። ማንም ሌላ የለም ። ይህን የጋዜጠኛ ነጻነት ሌላ ቦታ አገኘዋለሁ ብዬ አላምንም ። በዚህ ተመስገንን ሁሌም አከብረዋለሁ ። እውነት ለመናገር መቼም ወደ ፕሬስ ስራ ቢመለስ አብሬው ለመስራት የማላመነታው አንድ ሰው ይህ ዛሬ ታሰረ የተባለው ተመስገን ደሳለኝ ነው ። ለእኔ ለጋዜጠኛው ከመጽሔቱ ሰውየው ተመስገን ይበልጥብኛል ። እጄን ይዞ ሊያጽፈኝ የማይሞክር የነጻነት አለቃዬ ነው ። አክባሪዬም ነው ተመስገን ። ለእኔ ግን ከማክበሩም በላይ ነጻነቱ ይበልጥብኛል ። አሁንም ልድገመውና ተመስገን ነፃ ወጥቶ ወደ ፕሬስ ስራ ቢመለስ እስከ ነጻ ባለ ክፍያ አብሬው ለመስራት የምፈልገው ሰው ነው ። ነጻነት በራሱ ክፍያ ነው ። ተመስገን ደግሞ ይህን እንደሚከፍለኝ አምናለሁ ።
አምላክ በድጋሚ በስራ እንደሚያገናኘን ፀሎቴ ነው ።

Wednesday, October 1, 2014

የፓርቲዎቹ አባላት ጠበቃ ደረሰብኝ ባሉት ጫና ለጊዜው ሥራቸውን ማቆማቸውን አስታወቁ

በሕገመንግስቱ መሠረት ለደንበኞቼ አገልግሎት መስጠት አልቻልኩም፤ ከፍርድ ቤትና ከፖሊስም ማስፈራሪያ ደርሶብኛል ያሉት የአንድነት፣ የሰማያዊና የዓረና ፓርቲ አባላት ጠበቃ አቶ ተማም አባቡልጉ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ። ደንበኞቼ የምርመራ ቃላቸውን ለፖሊስ ከመስጠታቸው በፊት ላገኛቸው ሲገባ ይህ አልተደረገም ያሉት ጠበቃው፤ የጊዜ ቀጠሮው ችሎት እስኪጠናቀቅ ድረስ ለቀጣዩ አንድ ወር ደንበኞቻቸውን እንደማያገኙና ሕግን ባልጠበቀ መንገድ ለሚከናወን ተግባር የፕሮፓጋንዳ ሽፋን መሆን እንደማይፈልጉ አስታውቀዋል።


ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ለአንድነት ፓርቲ አባላቱ ለሀብታሙ አያሌውና ለዳንኤል ሺበሺ፤ ለአረናው አብርሃ ደስታ እና ለሰማያዊ ፓርቲው የሽዋስ አሰፋ ጠበቃ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኙ የነበሩ ሲሆን፤ ደረሰብኝ ባሉት ጫና እና ኢ-ሕገመንግስታዊ አሰራር ምክንያት ከደንበኞቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለጊዜውም ቢሆን ማቋረጣቸውን ለፓርቲዎቹ አመራሮች መግለፃቸውን አስረድተዋል። ይህም በመሆኑ ሦስቱ ፓርቲዎች (ማለትም አንድነት፣ ዓረና እና ሰማያዊ) በእስረኞቹ ላይ እየደረሰ ያለውን ኢ-ፍትሐዊ ድርጊት በተመለከተ ዛሬ መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም በአንድነት ቢሮ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።


እንደማንኛውም ጠበቃ ደንበኞቼን ማግኘት ቢኖርብኝም፤ ላገኛቸው አልቻልኩም፤ በፍርድ ቤት የምናቀርባቸው አቤቱታዎች እና ስሞታዎች በሙሉ ያለበቂ ምክንያት ውድቅ ይደረጉብናል፣ ይባስ ብሎም ኢ-ፍትሐዊ አሰራር በመኖሩ ለስርዓቱ ሕጋዊ ከለላ መሆን አልፈልግም የሚሉት አቶ ተማም አባቡልጉ፤ በዚህም ምክንያት የታሰሩት የፖለቲከኛ እስረኞች ምንም ዓይነት ሕጋዊ ከለላ ማግኘት አልቻሉም ሲሉ ነገ በሚደረገው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደሚያነሱ ምንጮች ጠቁመዋል።

በጥቅምት 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተጠርጣሪዎቹ በጊዜ ቀጠሮ ችሎት የሚቀርቡት ያለጠበቃ ቢሆንም፤ ምናልባትም ከወር በኋላ ዐቃቤ ሕግ ክስ የሚመሰርት ከሆነ፤ በችሎት ተገኝቼ ደንበኞቼን አገለግላለሁ የሚሉት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ፤ ደንበኞቼ ቃላቸውን ከመስጠታቸው በፊት እኔን ማግኘት ሲገባቸው ሳያገኙኝና ቃላቸውን ሰጥተው ከፈረሙ በኋላ ባገኛቸው ምን አደርግላቸዋለሁ? ሲሉ ጥያቄ አዘል ኀሳባቸውን ይሰነዝራሉ። ከዚህም ባሻገር ደንበኞቼ ከተጠረጠሩበት ጉዳይ ውጪ በሆነ መልኩ የሚደረግባቸው ምርመራ በፓርቲ ጉዳይ ላይ ሆኗል ሲሉ ቅሬታቸውን የሚያቀርቡት ጠበቃው፤ ለዚህም ጠንካራ አባል ማነው? የገንዘብ ምንጫችሁ ከየት ነው? የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው እንደነበር ደንበኞቼ ለፍርድ ቤት ቀርበውም አመልክተዋል ሲሉ ያስረዳሉ።

ይህም በመሆኑ የተላላኪነት ስራ ከመስራት ውጪ የምፈይደው ነገር የለም በሚል ለጊዜው ከደንበኞቼ ጋር መገናኘቱን አቁሜያለሁ ያሉት ጠበቃ ተማም፤ በዚህ አጋጣሚ ደንበኞችዎ ምን ሊያጋጥማቸው ይችላል ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፤ “የሚደርስባቸው ሁሉ ደርሶባቸዋል፤ እኔም ኖሬ ምንም አይነት የሕግ ከለላ አላገኙም” ሲሉ መልሰዋል።

የምጣዱ እያለ የእንቅቡን፤ የእርስ በርስ ግጭት እና የመንግስት ምላሽ

በያሬድ ሃይለማሪያም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች አሁንም ግጭቶች መበራከታቸው እና መፈናቀል መቀጠሉ የአገራችንን ፖለቲካ አሳሳቢ እያደረገው እና አገሪቱንም ወደ ችግር ውስጥ እየከተታት ይመስላል። መንግስት ለችግሮቹ የሚሰ...